 |
የካቶሊኩ ጳጳስ ወደ ኢትዮጵያን ለመውጋት የተዘጋጀውን ጦር እና ቦምቡ ሲባርክ |
Global Alliance for Ethiopia በመባል የሚታወቅ ማኅበር ነው፣ በዋናነት የፋሽስት ኢጣሊያ ጦር ቅድስት ሃገራችንን በእብሪተኝነት ወረራ ለማድረግ ሲነሳ የካቶሊክ ቤተክርስቲያን መድፉን ባርከው ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ እንዲጨፈጭፍ እና ብዙ እልቂት እንዲያደርስ ተባባሪ ሆነው በመገኘታቸው፥ በሃገራችን ኢትዮጵያም ከ60 ሺህ በላይ ንጹሐን ዜጎቻችን እንዲሁም ቅድስት ቤተክርስቲያናችን በግፍ ተመዝብራለች፣ ተቃጥላለች፣ ካህናት ታርደዋል ተረሽነዋል ከነዚህም ካህናት መካከል በዋናነት ሰማዕቱ ቅዱስ አቡነ ጴጥሮስ እንዲሁም አቡነ ሚካኤል እና በርካታ መነኮሳት ተረሽነዋል በግፍ ተገለዋል። የካቶሊካዊቱ ቤተክርስቲያን በፈጸመችው አስነዋሪ ተግባር ኢትዮጵያውያንን እና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንን ይቅርታ እንድትጠይቅ በሚል።
ከዚህ በተጨማሪ በየካቲት ፲፪ ቀን ፲፻፱፵፭ ዓም በርካታ ንጹሐን ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በመርዝ ጭስ የፈጀው የፋሺስቱ መሪ ግራዚያኒ የተመራው የኢጣሊያ ጦር በወቅቱ ጭፍጨፋ ለደረሰባቸው ንጹሐን ዜጎች ካሳ እንዲፍል ለማጠየቅ።
የሚከተለው የpetition ተዘጋጅቷል እና ይህንን በጎ ሀሳብ የምትስማሙ ወጎኖቻችን በሚከተለው ሊንክ በመጠቀም ትፈርሙ ዘንድ በታላቅ ትህትና እንገልጻለን።
እግዚአብሔር አምላክ ቅድስት ሃገራችንን እና ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን አሜን።
Petition ለመፈረብ ይህንን ይጫኑ
Let's save waldba! together
ዋልድባ እንታደግ!
No comments:
Post a Comment
እግዚአብሔር ያክብርልን ስለ አስተያየትዎ ከልብ እናመሰግናለን፡ መልሳችንን በቅርቡ ይጠብቁን፡ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችንም ጋር ይሁን አሜን፤