በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን
በሰሜን ጎንደር ሃገረ ስብከት ከሚገኘው የጠጣ መድኅኒዓለም የአንድነት ገዳም አንድ ጥሪ ደረሰን፣ ጥሪውም በገዳሙ ተወስነው የሚኖሩ አበው እንዲሁም እናቶች እራሳቸው ችለው በተለያየ ጊዜ ምዕመናን ከምናስቸግር በማለት አንድ ሥራ ለመሥራት በአካባቢው ከሚገኙ ነዋሪዎች ጋር በመተባበር ጥናት ተደርጎ የዳቦ መጋገሪያ ማሽን ለማቆም እና ከዚህ የሚገኘው ገቢ ለገዳሙ እለት ተዕለት ለሚደርሰው ውዳሴ አምላክ ለአገልግሎት ማስፈጸሚያ እጣን፣ ጧፍ እንዲሁም የተለያዩ አልባሳትን ለማሟላት ጥረት የሚያደርጉበት በመሆኑ የዝግጅት ክፍላክችም ይህንን የተቀደሰ ዓላማ ለመርዳት እና የበረከቱ ተካፋይ ለመሆኑ የሚያስቡ ምዕመናን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን አማኞች ይህንን ጥሪ ተቀብለው እጃቸውን እንድናሳስብላቸው ባደረሱልም መልዕክት ገልጸውልናል፥ እኛም የጉዳዩ ባለቤት ምዕመናን ናቸውና ጉዳዩን በቀጥታ ለባለጉዳዩ በማለት ለእናንተ በሚከተለው መንገድ አቅርበነዋል ተከታተሉት፡፡