Let's save waldba! together ዋልድባ እንታደግ!
በዓለም ዙሪያ ኢትዮጵያውያን
Tuesday, April 24, 2018
Abba Gebre Eyesus and Abba Gebre Selassie on VOA April 21, 2018
Let's save waldba! together ዋልድባ እንታደግ!
Sunday, April 15, 2018
ሚያዚያ ፭ ቀን ፳፻፲ VOA ከዋልድባ አባቶች እሥር በኃላ
Let's save waldba! together ዋልድባ እንታደግ!
Friday, April 13, 2018
በመጨረሻ አባቶቻችን ነፃ ተለቀዋል፥ አምላከ አበው የብዙዎችን ልቅሶ ተቀብሏል እንኳን ደስ አለን ለመላው ኢትዮጵያዊ በሙሉ
በመጨረሻም፣ በዐቃቤ ሕግ የተመሠረተባቸው የ“ሽብር ክሥ” የተቋረጠላቸው ኹለቱ የዋልድባ መነኰሳት ከእስር ተፈቱ፡፡
ዐቃቤ ሕግ፣ ከትላንት በስቲያ ረቡዕ ክሡን ማቋረጡን፣ ለፌዴራል ከፍተኛ ፍ/ቤት ልደታ ምድብ አራተኛ ወንጀል ችሎት ያስታወቀ ሲኾን፤ ተከሣሾቹ ለሚገኙበት ለቂሊንጦ እስር ቤት የመፍቻ ትእዛዝ እንዲጻፍለት በጠየቀው መሠረት ፍ/ቤቱ በሰጠው ትእዛዝ ኹለቱ አበው መነኰሳት ዛሬ፣ ሚያዝያ 5 ቀን 2010 ዓ.ም. ከእስር ተፈተዋል፡፡
ከአባ ገብረ ሥላሴ ወልደ ሃይማኖት ገብረ መድኅን ጋራ ለአንድ ዓመት ከአራት ወራት በእስር የቆዩት አባ ገብረ ኢየሱስ ኪዳነ ማርያም ካሴ(በፎቶው: በስተግራ የሚታዩት)፣ በዋልድባ አካባቢ የስኳር ፋብሪካ ለማቋቋም እንቅስቃሴ ከተጀመረበት ከ2004 ዓ.ም. አጋማሽ ጀምሮ፣ የገዳሙን ይዞታ ለማስከበር ማኅበረ መነኰሳቱን በመወከል ባደረጉት ጥረት ይታወቃሉ፡፡
ከኹለቱ አበው መነኰሳት ጋራ በአንድ መዝገብ የተከሠሠውና ከቃሊቲ እስር ቤት ጉዳዩን ሲከታተል የቆየው፣ አቶ ነጋ ዘላለም መንግሥቴም ከእስር የመፈቻ ትእዛዝ እንደወጣለት ተረጋግጧል፡፡ ከትላንት ጀምሮ ተፈጻሚ በኾነው የፍ/ቤቱ የፍች ትእዛዝ፣ ክሣቸው የተቋረጠላቸው 114 ተከሣሾች ከእስር እንደሚለቀቁ መዘገቡ ይታወሳል፡፡
Let's save waldba! together ዋልድባ እንታደግ!
Subscribe to:
Posts (Atom)