![]() |
የዋልድባ አበረንታንት አባቶች በሥራ ላይ |
በዋልድባ አበረንታንት
ገዳም የወሬ ዘመቻ ተከፍቶበታል
· ከዋልድባ ከ1000 በላይ መነኮሳት ተሰደዋል
· ብዙ መነኮሳት ተገለዋል
· የፋኖ ሃይል በገዳም በመግባት ድብደባ ፈጽሟል በማለት የሐሰት ዜናዎችን በማሰራጨት የተጠመዱ መነኮሳት በምዕራቡ አለም
ዋልድባ አበረንታንት ገዳም
ላለፉት 30 ዓመታት በርካታ ፈተናዎችን ማሳለፉን፣ በተለይ የቀድሞው የዘራፊው መንግሥት ኦርቶዶክሳውያንን ለመጉዳት ይልቁንም የሃይማኖታችንን
መሠረት የሆነውን የዋልድባ አበረንታንት ገዳምን እንዲነጥፍ ያላሰለሰ ጥረት ሲያድጉ መቆየታቸው የሚታወስ ነው፤ የሥኳር ፋብሪካን
እናቋቁማለን በሚል፣ የወርቅ ማውጫ በሚል፣ የእምነ በረድ ፋብሪካ እንገነባለን በሚል፣ የእጣን አዘጋጆች በሚል በተለያየ መልኩ ገዳሙን
እና ክብሩን ባልጠበቀ ሁኔታ ብዙ ደባ ሲፈጸም እንደነበረ የቅርብ ጊዜ ትውስታችን ነው።