![]() |
የገዳማውያኑ በረከት ይደርብን |
·
ዋልድባ ከምትመለሱ እናታችሁ ሆድ ብትገቡ ይቀላችኋል (አቶ ሲሣይ መሬሳ)
·
የሽሬ እና እንደስላሴ ሃገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የአቶ ሲሣይን አካሄድ መቃወም አለባቸው
·
የባሕር ዳር ሕዝበ ክርስቲያን እና የጎንደር ሕዝበ ክርስቲያን ሊመሰገኑ ይገባል
በፒዲፍ ለማንበብ እዚህ ይጫኑ
ባለፈው ሳምንት ከ30 - 40 የሚጠጉ መነኮሳት እና መነኮሳይት ከዋልድባ ገዳም በረሃ አቋርጠው
ለሚመለከተው ክፍል አቤት ለማለት፣ በእነ አቶ ሲሣይ እየደረሰባቸው ያለውን ግፍ ለማሳወቅ፣ ቤተክርስቲያናችንን ይተውልን በማለት
አቤት ለማለት ወደ ጎንደር ከዛም ወደ ባሕር ዳር የተጓዘው የመነኮሳቱ እና የመነኮሳይቱ ቡድን አቤቱታቸውን ለሚመለከተው የመንግሥት
አካላት እንዲሁም ለቤተክርስቲያኒቱ ለቀረቡት ሁሉ ብሶታቸውን ገዳማቸው (ገዳማችን) በጥቂት ጽንፈኞች በግፍ መነጠቁን ሲያሳውቁ ቆይተዋል፤
አሁንም በዚው ሥራቸው ላይ እንደሚገኙ ከአካባቢው የደረሰን መረጃ ያመለክታል።